1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

DW Amharic የነሐሴ 8 ቀን 2016 የዓለም ዜና

Eshete Bekeleረቡዕ፣ ነሐሴ 8 2016

ሶማሌላንድ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያን የምታሸማግለው ቱርክ ገለልተኛ አይደለችም ስትል ከሰሰች። የሶማሌላንድ ክስ የተደመጠው በአንካራ ለሁለተኛ ጊዜ የተካሔደው የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ውይይት ያለ ውጤት ከተበተነ በኋላ ነው። የሱዳንን ጦርነት ለማብቃት ያለመ ድርድር የብሔራዊው ጦር አዛዥ ጄነራል አብደል ፋታኅ አል-ቡርኻን በሌሉበት ተጀመረ። ግብጽ እና ሶማሊያ የወታደራዊ ትብብር ፕሮቶኮል ሥምምነት ተፈራረሙ። በጋዛ ውጊያ የገጠሙ ኃይሎች ተኩስ እንዲያቆሙ ለማድረግ ያቀደ ድርድር በቃጣር ሊካሔድ ነው። ጀርመን የኖርድ ስትሪም የጋዝ ማስተላለፊያን በማፈንዳት የጠረጠረችውን ግለሰብ ለመያዝ የእስር ማዘዣ አወጣች።

https://p.dw.com/p/4jTNy
ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ስለዚሕ ዝግጅት

ስለዚሕ ዝግጅት

PODC-DW-Amharisch-News-DWcom

የዓለም ዜና

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና የዜና ትንታኔዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ።